" በተኩሱ የተጠቁት ተሽከርካሪዎች ህጻናት ያሏቸው ወላጆችን ጨምሮ ሰላማዊ ሰዎችን ያሳፈሩ ነበሩ " - ነዋሪ
" በተኩሱ የተጠቁት ተሽከርካሪዎች ህጻናት ያሏቸው ወላጆችን ጨምሮ ሰላማዊ ሰዎችን ያሳፈሩ ነበሩ " - ነዋሪ በጋምቤላ ክልል አቦል ወረዳ፣ ከጋምቤላ ከተማ ወደ ኑዌር ዞን በእጀባ ሲጓዙ በነበሩ የህዝብ ተሽከርካሪዎች ላይ በተፈጸመ ተኩስ 16 ሰዎች መገደላቸውንና 57 ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ። ጥቃቱ መስከረም 8 ቀን 2019 ዓ.ም. ከቀኑ 7 ሰዓት ገደማ በአቦል ወረዳ አካባቢ መፈጸሙን ነዋሪዎቹ ገልጸዋል። በጥቃቱ የተሳተፉት ታጣቂዎች በህዝብ የተሞሉ ስድስት ተሽከርካሪዎች ላይ ተኩስ እንደከፈቱም ተናግረዋል። አንድ ነዋሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በስልክ በሰጡት መረጃ፣ " በታጣቂዎች የተገደሉት 16 ሰዎች ናቸው፤ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ደግሞ 57 ሰዎች ናቸው " ብለዋል። ሌላ ነዋሪ በበኩላቸው፣ 12 ሰዎች በጥቃቱ ቦታ ላይ ሲሞቱ፣ ሌሎች 4 ሰዎች ደግሞ በኋላ…
Read the full story at tikvahethiopia ↗