አሜሪካ ለውጭ አገር ተማሪዎችና ጋዜጠኞች የምትሰጠውን የቪዛ ፈቃድ የቆይታ ጊዜ ልታሳጥር ነው።
አሜሪካ ለውጭ አገር ተማሪዎችና ጋዜጠኞች የምትሰጠውን የቪዛ ፈቃድ የቆይታ ጊዜ ልታሳጥር ነው። የአሜሪካ የአገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት (DHS) የውጭ አገር ተማሪዎች፣ የባህል ልውውጥ ተሳታፊዎች እና ጋዜጠኞች በአገሪቱ ውስጥ ሊቆዩ የሚችሉበትን ጊዜ የሚገድብ አዲስ መመሪያ ማውጣቱን ሮይተርስ ዘግቧል። ከዚህ ቀደም እነዚህ የቪዛ ዓይነቶች ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን እስኪያጠናቅቁ ወይም ጋዜጠኞቹ የተመደቡበትን የሥራ ጊዜ እስኪጨርሱ ድረስ ያለምንም የጊዜ ገደብ እንዲቆዩ የሚፈቅዱ ነበሩ። በአዲሱ መመሪያ መሠረት የውጭ አገር ተማሪዎችና የባህል ልውውጥ ተሳታፊዎች በአሜሪካ ውስጥ መቆየት የሚችሉት ቢበዛ ለ4 ዓመታት ብቻ ይሆናል። ትምህርታቸውን ለማጠናቀቅ ተጨማሪ ጊዜ የሚያስፈልጋቸው ከሆነ አዲስ የቪዛ ማራዘሚያ ማመልከት ይኖርባቸዋል። በተጨማሪም ተማሪዎች ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ…
Read the full story at ayuzehabeshanews ↗