ተጨዋቾቹ ጠፉ‼

WASULIFEneutral2026-07-29 14:14:19 UTC
AdYour ad here[email protected]

ተጨዋቾቹ ጠፉ‼ ወደ ስዊድን ሀገር ለእግር ኳስ ጨዋታ ሄደው 20 ኢትዮጵያውያን ከነ ቡድን መሪያቸው በዚያው መጥፋታቸው ተሰማ። ​በስዊድን በተካሄደው የጎቲያ ካፕ የእግር ኳስ ውድድር ላይ ከተሳተፉ ከ20 በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች እና የቡድን መሪዎች በዚያው መጥፋታቸውን የስዊድን ፖሊስ አስታውቋል። ​ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 17 የሚሆኑት እነዚህ ታዳጊዎች በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ያረፉበት ትምህርት ቤት ያለምንም ማስጠንቀቂያ ለቀው መሄዳቸው ተውቋል። ​የስዊድን ፖሊስ ጉዳዩን አጣርቶ ግለሰቦቹ ወደ ኢትዮጵያ አለመመለሳቸውን እና መጥፋታቸው በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ እንጂ ህገወጥ የሰዎች ዝውውር ምልክት እንደሌለው ገልጿል። ​እስካሁን ድረስ የኢትዮጵያ መንግስትም ሆነ በስዊድን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ስለ ጉዳዩ የሰጡት አስተያየት የለም። #WasuMohammed video…

Read the full story at wasulife ↗
AdYour ad here[email protected]