ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት ይቀጥሉ ‼ - የአሜሪካ ሴኔት
ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት ይቀጥሉ ‼ - የአሜሪካ ሴኔት የአሜሪካ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት (የላይኛው ምክር ቤት፣ ሴኔት)ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ ስልጣናቸውን ለማገድ የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ በ 49 ለ 50 በሆነ በጠበበ የድምፅ ልዩነት ውድቅ አደረገ። በሴናተር ኪርስተን ጊሊብራንድ የቀረበው ይህ ጥያቄ፣ ኮንግረሱ የጦርነት አዋጅ ሳያወጣ የአሜሪካ ጦር በኢራን ውስጥ የሚያደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንዲያቆም የሚጠይቅ ነበር። ውሳኔው ውድቅ መደረጉን ተከተሎ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በቀጣናው ላይ ያላቸው ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ ሙሉ ስልጣን እንደተጠበቀ ይቆያል። በድምፅ አሰጣጡ ላይ ሦስት የሪፐብሊካን ዓባላት ሃሳቡን ሲደግፉ፣ አንድ የዲሞክራቲክ አባል ደግሞ ተቃውሞ ድምፅ ሰጥቷል። @Addis_News @Addis_News
Read the full story at addis_news ↗