ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት ይቀጥሉ ‼ - የአሜሪካ ሴኔት

ADDIS_NEWSneutral2026-07-31 06:07:28 UTC
AdYour ad here[email protected]

ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት ይቀጥሉ ‼ - የአሜሪካ ሴኔት የአሜሪካ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት (የላይኛው ምክር ቤት፣ ሴኔት)ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ ስልጣናቸውን ለማገድ የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ በ 49 ለ 50 በሆነ በጠበበ የድምፅ ልዩነት ውድቅ አደረገ። ​በሴናተር ኪርስተን ጊሊብራንድ የቀረበው ይህ ጥያቄ፣ ኮንግረሱ የጦርነት አዋጅ ሳያወጣ የአሜሪካ ጦር በኢራን ውስጥ የሚያደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንዲያቆም የሚጠይቅ ነበር። ​ውሳኔው ውድቅ መደረጉን ተከተሎ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በቀጣናው ላይ ያላቸው ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ ሙሉ ስልጣን እንደተጠበቀ ይቆያል። ​በድምፅ አሰጣጡ ላይ ሦስት የሪፐብሊካን ዓባላት ሃሳቡን ሲደግፉ፣ አንድ የዲሞክራቲክ አባል ደግሞ ተቃውሞ ድምፅ ሰጥቷል። ‎ @Addis_News @Addis_News

Read the full story at addis_news ↗
AdYour ad here[email protected]