''ወደ መቐለ ለመግባት ዝግጅት አጠናቀናል" የትግራይ የሰላም ሃይል
''ወደ መቐለ ለመግባት ዝግጅት አጠናቀናል" የትግራይ የሰላም ሃይል እራሱን 'የትግራይ የሰላም ሃይል' ብሎ የሰየመው እና በቀድሞ የሕወሓት/ትሕነግ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች (በወዲ አንጥሮ፣ ጀነራል ጉዕሽ ገብረ እና ጀነራል ከበደ ፍቃዱ) የሚመራው ታጣቂ ቡድን፤ ሕወሓትን ከመቐለ አስወጥቶ ከተማዋን ለመቆጣጠር የሚያስችለውን ዝግጅት ማጠናቀቁን የወታደራዊ አዛዡ ገለጹ። አዛዡ አክለውም በርካታ የታጣቂ ቡድኑ አባላት ሕወሓትን እየከዱ እጃቸውን እየሰጡ መሆኑንና ይህም የቡድኑን መዋቅር በማፍረስ በቀላሉ ለመቆጣጠር ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ማለታቸውን ዘገባው ያመለክታል። በተያያዘ መረጃ ሌ/ጄኔራል ፃድቃን ገብረተንሳይ "በአንድ ወር ልንገባ እንችላለን እኔ ትልቅ ተስፋ አለኝ ምክንያቱም በትግራይ ያለው ኃይል በፖለቲካ ተሸንፏል፣ሃይላችንን መሰብሰብና መምታት ብቻ ነው የቀረን" ማለታቸው ይታወሳል…
Read the full story at wasulife ↗