አበባየሁ ደሜ በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ሥር ዋለ።
አበባየሁ ደሜ በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ሥር ዋለ። “የሀገር መከላከያ ሰራዊት አልባሳት በመጠቀም በየማህበራዊ ሚዲያው አላስፈላጊ መልእክቶችን እንዲሁም የአንድነትና የፍቅር ሀሳብ ከማስተላለፍ ይልቅ የመከፋፈል ንግግሮችን ሲያሰራጭ ነበረ” የተባለው አበባየሁ ደሜ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል። አበባየሁ ደሜ ዛሬ ከሰአት አካባቢ ሜክሲኮ ኬ ኬር ህንፃ ወረድ ብሎ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ መወሰዱ ተረግጧል። ግለሰቡ በሀገር ጥበቃ እና ክብር መገለጫ በሆነው የመከላከያ አልባሳት በየሚዲያው እየቀረበ የሚያደርገው እንቅስቃሴ በብዙዎች ዘንድ ቅሬታን እና እርስ በእርስ የመከፋፈል ስሜትን ሲፈጥር መቆየቱ ተዘግቧል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
Read the full story at addis_reporter ↗