ኢትዮጵያ በውድድሩ የመጀመሪያዋን ወርቅ አግኝታለች።
ኢትዮጵያ በውድድሩ የመጀመሪያዋን ወርቅ አግኝታለች። ኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች የዓለም ሻምፒዮና የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አስመዘገበች። በአሜሪካ ኦሪገን እየተካሄደ ባለው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና፤ በሴቶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር ኢትዮጵያ የወርቅና ብርና ሜዳሊያ አግኝታለች። አትሌት አልማዝ ዮሃንስ ርቀቱን በ9:15.81 በሆነ ጊዜ ቀዳሚ በመሆን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝታለች። አትሌት ወሰኔ አሰፋ ደግሞ 9:30.50 በሆነ ጊዜ በመግባት ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ የብር ሜዳሊያ ባለቤት ሆናለች። ኢትዮጵያ እስካሁን በውድድሩ አንድ የወርቅ ፣ ሁለት የብር እና አንድ የነሀስ ሜዳልያ አግኝታለች። #አሚኮ #Ethiopia #WirldAthletics
Read the full story at amharamassmedia ↗