በኤሌክትሪክ የሚሰራ ሳይክል የተገጩት የጣልያኗ ኮሞ ከተማ ከንቲባ ከእንግዲህ በከተማዋ ሳይክል እንዳይነዳ አገዱ።

ADDIS_NEWSneutral2026-08-21 13:01:57 UTC
AdYour ad here[email protected]

በኤሌክትሪክ የሚሰራ ሳይክል የተገጩት የጣልያኗ ኮሞ ከተማ ከንቲባ ከእንግዲህ በከተማዋ ሳይክል እንዳይነዳ አገዱ። ከንቲባ አሌሳንድሮ ራፒንስ ጅምላ እገዳው የተጣለው የከተማዋና ሕዝብ ደህንነት ለማረጋገጥ ነው ብለዋል። በከንቲባው ውሳኔ መሰረት ከቀናት በኋላ በአነስተኛ ከተማዋ 30 ጐዳናዎች ላይ ሳይክል ጋላቢዎች ዝር እንዲሉ አይፈቀድላቸውም። ከንቲባ ራፒንስ ለጣልያን ዜና አገልግሎት እንደነገሩት ሰዎች ከልምዳቸው ተነስተው ነው ውሳኔ የሚሰጡት እኔም በእነዚህ አውሬ ሳይክሎች የደረሰብኝን አውቀዋለሁ ብለዋል። በሌላ በኩል በርካታ የአውሮፓ ከተሞች የኤሌክትሪክ ሳይክሎች የትና እንዴት እንደሚጋለቡ የሚወስን ድንጋጌ ያወጡ ሲሆን በሌላ በኩል ሰዎች በእግራቸው የሚያሽከረክሯቸው ሳይክሎች ግን እገዳ አልተጣለባቸውም። @Addis_News @Addis_News

Read the full story at addis_news ↗
AdYour ad here[email protected]