አንዲት እናት በሳውላ አጠቃላይ ሆስፒታል በአንድ ጊዜ አራት ሴት ህፃናትን በሰላም ተገላገለች

ADDIS_NEWSneutral2026-08-30 12:00:20 UTC
AdYour ad here[email protected]

አንዲት እናት በሳውላ አጠቃላይ ሆስፒታል በአንድ ጊዜ አራት ሴት ህፃናትን በሰላም ተገላገለች ​በጎፋ ዞን ሳውላ አጠቃላይ ሆስፒታል አንዲት እናት በአንድ ጊዜ አራት ህፃናትን በሰላም መገላገሏ ተነገረ። ​በሳውላ አጠቃላይ ሆስፒታል ተገቢው ምርመራ ከተደረገላት በኋላ ለተከታታይ አምስት ቀናት በቅርብ የሕክምና ክትትል ስር ቆይታ ወሊዱን ያከናወነችው እናት፣ በአሁኑ ወቅት ከነሙሉ ጤንነታቸው ከ አራቱም ህፃናት ጋር በጥሩ ሁኔታ ላይ ትገኛለች። ​የማህጸንና ጽንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ግላንደ ጊሎ እንደገለጹት፣ በሆስፒታሉ ደረጃ ሁለት እና ሦስት ህፃናትን በአንድ ጊዜ ማዋለድ የተለመደ ቢሆንም፣ በአንድ ወሊድ አራት ህፃናትን በሰላም ማዋለድ መቻሉ በሆስፒታሉ ታሪክ የመጀመሪያው ነው። ​የህፃናቱ አባት አቶ ናፍቆት ቡሼ በበኩላቸው፣ ከዚህ ቀደም የአምስት ሴት ልጆች አባት እንደነበሩ አጋልጠው፤…

Read the full story at addis_news ↗
AdYour ad here[email protected]